ፈሥሒ ኦ ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ ቅድስት ወንጽሕት ሰአሊተ አማን በእንተ እጓለ እመሕያው። ተፈሥሒ።
በእውነት ለሰው ወገን አማላጅ የምትሆኚ አምላክን የወለድሽ ንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ ደስ ይበልሽ። ደስ ይበልሽ።
Rejoice, O Virgin Mary, parent of God, holy and pure, very pleader for the race of mankind. Rejoice.
አሊ ለነ ቅድመ ክርስቶስ ወልድኪ ከመ ይጸግወነ ስርየተ ኃጢአትነ። አሜን።
የኃጢአታችንን ስርየት ይሰጠን ዘንድ በልጅሽ በክርስቶስ ፊት ለምኚልን። አሜን።
Plead for us before Christ thy Son, that He may vouchsafe us remission of our sins. Amen.
ፈሥሒ ኦ ድንግል ንጽሕት ንግሥት በአማን። ተፈሥሒ። ተፈሥሒ ኦ ትምክህተ ዘመድነ። ተፈሥሒ።
በእውነት ንግሥት የምትሆኚ ንጽሕት ድንግል ሆይ ደስ ይበልሽ። ደስ ይበልሽ። የባሕርያችን መመኪያ ሆይ ደስ ይበልሽ። ደስ ይበልሽ።
Rejoice, O Virgin pure, very Queen. Rejoice. Rejoice, O pride of our kind. Rejoice.
ፈሥሒ ኦ ዘወለድኪ ለነ አማኑኤል አምላክነ። ተፈሥሒ።
አምላካችንን አማኑኤልን የወለድሽልን ሆይ ደስ ይበልሽ። ደስ ይበልሽ።
Rejoice, O thou that barest for us Emmanuel our God. Rejoice.
ስእለኪ ከመ ተሐዝኚነ ኦ አማናዊት መስተዓርቅት ቅድመ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ከመ ይገብር ምሕረተ ለነፍሳተነ ወይሥረይ ለነ ኃጢአተነ። አሜን።
በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ፊት እውነተኛ አስታራቂ ሆነሽ ታስቢን ዘንድ እንለምንሻለን፤ ለነፍሳችን ይቅርታን ያደርግልን ዘንድ ኃጢአታችንንም ያስተሰርይልን ዘንድ። አሜን።
We ask thee to remember us, O true Mediatrix, before our Lord Jesus Christ that He may have mercy upon our souls and forgive us our sins. Amen.
ንቱ ውእቱ ጊዜ ባርኮት ወዝንቱ ውእቱ ጊዜ ዕጣን ኅሩይ ጊዜ ስብሐተ ፈጣሪነ መፍቀሬ ሰብእ ክርስቶስ።
የሚመሰገን ጊዜ ይህ ነው፤ የተመረጠ የዕጣን ጊዜም ይህ ነው፤ ሰውን ወዳጅ መድኃኒታችንን ክርስቶስን ማመስገኛ ነው።
This is the time of blessing; this is the time of chosen incense, the time of the praise of our Savior, lover of man, Christ.
ርያም ይእቲ ዕጣን ወዕጣን ውእቱ እስመ ዘውስተ ከርሣ ዘይትሜዐዝ እምኵሉ ዕጣን ዘወለደቶ መጽአ ወአድኃነነ።
ማርያም ናት ዕጣን፤ ዕጣን እርሱ ነው፤ በማኅፀኗ ያደረ ከታጠበው ዕጣን ሁሉ የሚሸት ነውና፤ የወለደችው መጥቶ አዳነን።
Mary is the incense, and the incense is He, because he who was in her womb is more fragrant than all chosen incense. He whom she bare came and saved us.
ፍረት ምዑዝ ኢየሱስ ክርስቶስ ንዑ ንስግድ ሎቱ ወንዕቀብ ትእዛዛቲሁ ከመ ይሥረይ ለነ ኃጢአተነ።
ኢየሱስ ክርስቶስ መዓዛ ያለው ሽቱ ነው፤ ኑ እንስገድለት ትእዛዛቱንም እንጠብቅ ኃጢአታችንን ያስተሰርይልን ዘንድ።
The fragrant ointment is Jesus Chris. O come let us worship Him and keep His commandments that He may forgive us our sins.
ውህቦ ምሕረት ለሚካኤል ወብሥራት ለገብርኤል ወሀብተ ሰማያት ለማርያም ድንግል ዘያብጽሓ ውስተ መንግሥት።
ለሚካኤል ምሕረት ተሰጠው፤ ለገብርኤልም ማብሰር ተሰጠው፤ ለድንግል ማርያምም ወደ መንግሥተ ሰማያት የምትገባበት ሀብት ተሰጣት።
To Michael was given mercy, and glad tidings to Gabriel, and a heavenly gift to the Virgin Mary.
ውህቦ ክብር ለዳዊት ወጥበብ ለሰሎሞን ወቀረነ ቅብዕ ለሳሙኤል እስመ ውእቱ ይቀብዕ ነገሥተ።
ለዳዊት ክብር ለሰሎሞንም ጥበብ ለሳሙኤልም ነገሥታትን የቀባ እርሱ ነውና የሽቱ ቀንድ ተሰጠው።
To David was given understanding, and wisdom to Solomon, and an horn of oil to Samuel for he was the anointer of kings.
ውህቦ መራኁት ለእግዚእነ ጴጥሮስ ወድንግልና ለዮሐንስ ወመልእክት ለእግዚእነ ጳውሎስ እስመ ውእቱ ብርሃነ ቤተ ክርስቲያን።
ለአባታችን ለጴጥሮስ መክፈቻ ለዮሐንስም ድንግልና ተሰጠው፤ ለአባታችን ለጳውሎስ የቤተክርስቲያን ብርሃን እርሱ ነውና መላእክት ተሰጠው።
To our father Peter were given the keys, and virginity to John, and apostleship to our father Paul, for he was the light of the church.
ፍረት ምዑዝ ይእቲ ማርያም እስመ ዘውስተ ከርሣ ዘይትሜዐዝ እምኵሉ ዕጣን መጽአ ወተሠገወ እምኔሃ።
መዓዛ ያላት ሽቱ ማርያም ናት፤ በማኅፀኗ ያደረው ከአማኝ ሁሉ የሚበልጥ ነውና መጥቶ ከእርሷ ሰው ሆነ።
The fragrant ointment is Mary, for he that was in her womb, who is more fragrant than all incense, came and was incarnate of her.
ማርያም ድንግል ንጽሕት ሠምረ አብ ወአሠርገዋ ደብተራ ለማኅደረ ፍቁር ወልዱ።
ንጽሕት ድንግል ማርያም አብ ወደዳት፤ ከተወደደ ልጁ ማደሪያ ትሆን ዘንድ በንጽሕና አስጌጣት።
In Mary virgin pure the Father was well-pleased, and he decked her to be a tabernacle for the habitation of his beloved Son.
ውህቦ ሕግ ለሙሴ ወክህነት ለአሮን ተውህቦ ዕጣን ኅሩይ ለዘካርያስ ካህን።
ለሙሴ ሕግ ለአሮንም ክህነት ተሰጠው፤ ለካህኑ ለዘካርያስም የተመረጠ ዕጣን ተሰጠው።
To Moses was given the law, and priesthood to Aaron. To Zacharias the priest was given chosen incense.
ብተራ ስምዕ ገብርዋ በከመ ነገረ እግዚእ ወአሮን ካህን በመካከላ ያዐርግ ዕጣነ ኅሩየ።
የምስክር ድንኳን አደረጉት ጌታ እንደተናገረ፤ ካህኑ አሮን በመካከሏ የተመረጠውን ዕጣን ያሳርጋል።
They made a tabernacle of testimony according to the word of God; and Aaron the priest, in the midst thereof, made the chosen incense to go up.
